የአሜሪካ እና ኢራን ቴክኒካዊ ንግግር በሚቀጥለው ሳምንት ድጋሚ እንደሚጀመር ተገለጸ
የአሜሪካ እና ኢራን ቴክኒካዊ ንግግር በሚቀጥለው ሳምንት በድጋሚ እንደሚጀመር የአሸማጋይዋ ፓኪስታን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ።
“ምናልባት ማክሰኞ” ዕለት ይጀመራል የተባለው ቀጣዩ ቴክኒካዊ ንግግር የሚካሄድበት ቦታ ግን ይፋ አልተደረገም።
ስዊትዘርላድ ውስጥ የተካሄደው የሁለቱ አገራት የመጀመሪያው ዙር ንግግር እሁድ ዕለት ከተጠናቀቀ በኋላ የሁለቱ አገራት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ስዊዘርላንድን ለቅቀው ሄደዋል።
የቴክኒካል ልዑካኖቻቸው ግን ሰኞ ዕለትም ንግግር ማድረግ ቀጥለው ነበር።
ማክሰኞ ዕለት የኢራን የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትር ካዜም ኸሪባባዲ የመጀመሪያው ዙር የቴክኒካል ንግግር መጠናቀቁን አስታውቀዋል።
ተደራዳሪዎቹ “የማዕቀብ መነሳት”፣ “የኒውክሌር ጉዳይ”፣ “የኢኮኖሚ መልሶ ግንባታ እና ልማት” እንዲሁም “የቁጥጥር እና ትግበራ” ጉዳዮች ላይ የሚሰሩ አራት ቡድኖችን ማቋቋማቸውንም ገልጸዋል።
እነዚህ የስራ ቡድኖች አሜሪካ እና ኢራን የፈረሙትን የመግባቢያ ስምምነት ቴክኒካዊ ዝርዝር ጉዳዮች አፈጻጸምን የመከታተል ኃላፊነት ይኖራቸዋል።